ክቡር አቶ ተስፋዬ ንዋይ እንግዳሸት በአሁኑ ወቅት የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ /ቤት ምክትል ፕሬዝዳንት እና የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ፍርድ ቤቶች ቃል አቀባይ በመሆን እያገለገሉ ይገኛሉ፡፡

አቶ ተስፋዬ የሕግ አገልግሎት የጀመሩት በኦሮሚያ ክልል የወረዳ አቃቤ ሕግ ቢሮ ኃላፊ በመሆን ነበር፡፡ ከዚህ በመቀጠል ለሦስት ዓመታት ያህል በኦሮሚያ የሕግ ባለሙያዎች ሥልጠናና በሕግ ምርምር ኢንስቲትዩት ከፍተኛ የሕግ ተመራማሪ ሆነው አገልግለዋል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ በኢትዮጵያውድድር እና የሸማቾች ጥበቃ ፍርድ ቤት ሰብሳቢ ዳኛ በመሆን ከሁለት ዓመት በላይ አገልግለዋል፡፡ ከዚህ በመቀጠል በኢትዮጵያ የመንግስት የልማት ድርጅቶች ሚኒስቴር የሚኒስትር አማካሪ ሆነው ሊሾሙ ችለዋል፡፡ 

አቶ ተስፋዬ ከመደበኛ ስራቸው ጎን ለጎን ህብረተሰቡን ሊያስተምሩና ግንዛቤን ሊያሳድጉ የሚችሉ ሶስት መፅሀፍትን በመጻፍ አሳትመዋል፡፡ መፅሀፎቹም ‹የፕሮጀክት አመራር ሳይንስ እና ጥበብ›ሕግ እና አተረጓ እና የንግድ ወድድርና ሸማቾች ጥበቃ ህጋዊና ኢኮኖሚያዊ ገፅታ የሚል ርዕስ አላቸው፡፡  

አቶ ተስፋዬ የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ /ቤቶች ቃል አቀባይ በመሆን ከተሾሙ በኋላ በፌዴራል /ቤቶች እና በፍትህ አካላት ማሻሻያ በተነሱ ጉዳዮች ላይ በርካታ ንግግሮችን አቅርበዋል፡፡ በተጨማሪም መጣጥፎችን ለጋዜጦች በማበርከት የህግ መጣጥፎች እንዲዳብሩ ለማድረግ ከፍተኛ ጥረት እያደረጉ ይገኛሉ፡፡

አቶ ተስፋዬ የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን በህግ ከመቀሌ ዩኒቨርስቲ በመቀጠል  ሁለተኛ ዲግሪያቸውን በፕሮጀክት ማኔጅመንት ከቻይናው ዩናን ፋይናንስና ኢኮኖሚክስ ዩኒቨርሲቲ በማዕረግ አግኝተዋል፡፡

                           

ክብርት ወ/ሮ አሸነፈች አበበ አሊቤ ሰኔ 12 ቀን 1978 ዓ.ም አዲስ አበባ ውስጥ ተወልደው ያደጉ ሲሆን በአሁኑ ሰዓት  በፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ /ቤት በምክትል ፕሬዝዳንትነት እያገለገሉ የሚገኙ ይገኛሉ፡፡ 

ወ/ሮ አሸነፈች በሕግ መስክ በቂ ልምድ ያላቸው ሲሆን ከአራት ዓመት በላይ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የፍትህ ቢሮ የሕግ ማርቀቅ እና ምርምር ኦፊሰር እንዲሁም በጠቅላይ ዓቃቤ ህግ በዐቃቤ ህግነት አገልግለዋል፡፡ ከዚህ በመቀጠል በዳኝነት ተሾመው ከስድስት ዓመት በላይ በአዲስ አበባ ከተማ /ቤት እና በፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ /ቤት አገልግለዋል፡፡ 

ወ/ሮ አሸነፈች በህግ የመጀመሪያ ዲግሪ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ እንዲሁም የመጀመሪያ ዲግሪ በሊደርሺፕ ከሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ አግኝተዋል፡፡