የህጻናት ፍትህ ኘሮጀክት ጽ/ቤት

የህጻናት ፍትህ ኘሮጀክት ጽ/ቤት በፍትህ ስርዓቱ ውስጥ የሚያልፉ የህጻናትን ጥቅምና ደህንነት ለማስጠበቅ በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ስር የተቋቋመ ጽ/ቤት ነው፡፡ማዕከሉ ከ18 አመት በታች ለሆኑና በፍትህ ስርዓቱ ውስጥ ለሚያልፉ ህጻናት በሙሉ አገልግሎቱን ያለምንም ክፍያ በነፃ ይሰጣል፡፡

ማዕከሉ የሚሰጠው አገልግሎቶች

  • የመክፈል አቅም ለሌላቸው ህጻናትና የህፃናቱን ጉዳይ ይዘው ለሚመጡ ባለጉዳዮች ነፃ የሕግ ድጋፍ መስጠት
  • በፍርድ ቤትም ሆነ ከፍርድ ቤት ውጪ ለህፃናት መብትና ደህንነት መሟገት
  • መንግስታዊና መንግስታዊ ካልሆኑ ተቋማት ጋር በመቀናጀት የማህበራዊና ስነልቦናዊ ድጋፍ መስጠት
  • በፍትህ ስርዓቱ ውስጥ ከሚያልፉ ህፃናት ጋር በቅርብ ለሚሰሩ አካላት የአቅም ግንባታ ስልጠና መስጠት
  • በፍ/ቤት ትዕዛዝ በመሰረት የዘረመል (DNA) ምርመራ እንዲካሄድ ድጋፍ መስጠት
  • የማማከር አገልግሎት መስጠት

የሕግ ምክር አገልግሎት አይነቶች

  • የቃል ምክክር
  • አስፈላጊውን የፍርድ ቤት አቤቱታ፣ ማመልከቻና ቃለ መሐላ ማዘጋጀት
  • የጥብቅና አገልግሎት መስጠት
  • በባለሙያ የታገዘ የማስማማት አገልግሎት
  • ለህግ አስፈፃሚ አካላት ተገቢውን የድጋፍ ደብዳቤና አቤቱታ መፃፍ

የማህበራዊና ስነልቦናዊ ድጋፎች
 

መንግስታዊና መንግስታዊ ካልሆኑ ተቋማት ጋር በመቀናጀት የማህበራዊና ስነልቦናዊ የሚሰጡበት አገልግሎት አይነቶች፤

  • የምግብ፣የመጠለያ፣የትምህርት እና የትራንስፖርት ድጋፍ
  • የስነልቦና ምክር
  • የገቢ ማስገኛ ኘሮግራም
  • ከቤተሰብ ጋር ማቀላቀል

አገልግሎቱ የሚሰጥባቸው ቦታዎች

  • በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የህጻናት ፍትህ ኘሮጀክት ጽ/ቤት
  • በፌዴራል ከፍተኛ ልደታ ምድብ ችሎት
  • በፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የካ እና ንፋስ ስልክ ላፍቶ ምድብ ችሎቶች