የፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የአፈፃፀም ሁኔታ ማደጉ ተገለፀ፡፡ *************************************************

20

የፌዴራል ፍርድ ቤቶች ዋና ራዕይ የዳኝነት ስርዓቱን አዘምኖ ቀልጣፋ፣ ፍትሐዊ፣ ተገማች፣ ከአድሎ የነፃ የዳኝነት አገልግሎት በመስጠት የህዝብ አመኔታን መገንባት ነው፡፡ ፍርድ ቤቶች የህዝብ አመኔታን ከመገንባት አንፃር ራዕይውን እውን ሊያደርጉ የሚችሉ መመሪያዎችን ከማዘጋጀት ጀምሮ የዳኝነት ተደራሽነትን ከማረጋገጥ፣ የቴክኖሎጂ ተጠቃሚነትን ከማስፋት፣ የሰራተኞችን የአገልጋይት መንፈስ ከማሳደግ እንዲሁም ምቹ የስራ ሁኔታን ከመፍጠር አንፃር ከፍተኛ ስራዎችን እየሰሩ ይገኛሉ፡፡

የፌዴራል ፍርድ ቤቶች የፍርድ ቤት መር አስማሚነትን አጠንክረው ሊሰሩ እንደሚገባ ተገለጸ፡፡ ***********************************************************************************

29

የፌዴራል ፍርድ ቤቶች አንድ የለውጥ አካል አድርገው እየሰሩባቸው ከሚገኙ ጉዳዮች አንዱ የፍርድ ቤት መር አስማሚነት ነው፡፡ የፍርድ ቤት መር አስማሚነት ለፍርድ ቤቶች ስራዎችን ከማቀላጠፍና ውጤታማ ስራዎችን ከመከወን አንፃር ያለው ሚና የጎላ በመሆኑ በ2014 ዓ.ም መመሪያ (መመሪያ ቁጥር 12/2014) ተዘጋጅቶለት ወደ ስራ ተገብቷል፡፡  ይህን ተከትሎ የፍርድ ቤት መር አስማሚነትን የፌዴራል ፍርድ ቤቶች በሚፈልጉት ልክ ይፈፀም ዘንድ ለዳኞች፣ ለረዳት ዳኞች፣ ለሬጅስትራሮች እና ከስራው ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት ላላቸው ባለሙያዎች የእውቀትና የክህሎት ማሳደጊያ ስልጠናዎችን እየሰጠ ይገኛል፡፡

ለፌዴራል ፍርድ ቤቶች ሲሰጥ የቆየው የኤሌክትሮኒክስ ግዥ (E-GP) ስልጠና ተጠናቀቀ፡፡

36

መንግስት የመንግስት ባለበጀት መስሪያ ቤቶችን የግዥ ስርዓት ለማዘመንና በግዥ ሂደት የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመፍታት የኤሌክትሮኒክስ የግዥ (E-GP) ስርዓትን እንዲተገብሩት የማስቻል ስራ እየሰራ ይገኛል፡፡  ይህን የግዥ ስርዓት ቀድመው ከተገበሩት ተቋማት ደግሞ የፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ይገኝበታል፡፡ ፍርድ ቤቱ ከአለው የስራ ባህሪ እና የስራ ውስብስብነት አንፃር የኤሌክትሮኒክስ (E-P) ግዥን እንዲተገብሩ ከመዘገቡት ተቋማት ውስጥ ባይካተትም የግዥ ስርዓቱ አስፈላጊ ከመሆኑና ፍርድ ቤቱ የያዘውን ራዕይ ለማሳካት ያለው አስተዋፅዖ ከፍተኛ በመሆኑ በፈቃደኝነት ወደ ስራው ሊገባ ችሏል፡፡

የፌዴራል መጀመሪያ ፍርድ ቤት የግዥ ሂደትን ውጤታማ ለማድረግ እየሰራ መሆኑ ተገለፀ፡፡

34

ይህ የተነገረው የመንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር ባለስልጣን የመንግስት የኤሌክትሮኒክስ ግዥ ስርዓትን ማስፈን ስለሚሰጠው ጥቅም ለፌዴራል ፍርድ ቤቶች በተለይም የመንግስት የኤሌክትሮኒክስ ግዥ ስርዓትን በመተግበር ላይ ለሚገኘው የፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ለፕሬዘዳንቶች፣ ተጠሪ ዳኞች፣ ዳይሬክተሮች፣ ስራ ክፍል ሀላፊዎች እና ከስራው ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት ላላቸው ባለሙያዎች ምክክር መድረክ በሚሰጥበት ወቅት ነው፡፡

በቅሬታ አቀራረብ እና አፈታት ዙሪያ ስልጠና ተሰጠ፡፡

71

በሰራተኞች ቅሬታ አቀራረብ እና የቅሬታ ሰሚ ኮሚቴ ሚና ዙሪያ ለፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አመራሮች፣ ለተጠሪ ዳኞች፣ ለአስተባበሪ ሬጅስትራሮች፣ ለዳይሬክተሮች፣ ለስራ ክፍል ሃላፊዎች እና ለቅሬታ ሰሚና ዲሲፐሊን ኮሚቴ አባላት መጋቢት 08/2015 ዓ.ም በአዜማን ሆቴል ስልጠና ተሰቷል፡፡

በድሬዳዋ ም/ችሎት የግማሽ ዓመት የእቅድ አፈጻጸም ውይይት ተደረገ

41

የፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በስሩ የሚገኙ ምድብ ችሎቶችን የ2015 በጀት ዓመት የግማሽ ዓመት የእቅድ አፈጻጸም በየደረጃው ገምግሟል፡፡ ፍርድ ቤቱ የድሬዳዋ ም/ችሎትን የተናጠል የእቅድ አፈጻጸም የካቲት 25/2015 ዓ.ም በኒው ብሎሰም ሆቴል- ድሬዳዋ ገምግሟል፡፡

ለአስተዳደር ሰራተኞች ስልጠና ተሰጠ፡፡

93

የፌዴራል ፍርድ ቤቶች የዳኝነት ተደራሽነትን፣ ቀልጣፋና ጥራት ያለው የዳኝነት ስርዓትን፣ ተገማች ፍርድን እንዲሁም ቴክኖሎጂ ተጠቃሚነትን ተቋማዊ  እሴት በማድረግ  የህዝብ አመኔታን ያተረፈ የዳኝነት ተቋም ለመገንባት ከፍተኛ ስራ እያከናወኑ ይገኛሉ፡፡ ከእነዚህ ውስጥ አንዱ የዳኞችና የአስተዳደር ሰራተኞችን የመፈጸም አቅም ለማሳደግ  ትምህርትን ጨምሮ የተለያዩ የአጭር እና የረጅም ጊዜ ስልጠናዎችን መስጠት ይገኝበታል፡፡

የፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የህፃናት ችሎቶችን እያዘመነ መሆኑ ተገለጸ፡፡

73

የፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ካደራጃጀው ችሎቶች አንዱ የህፃናት ችሎት ነው፡፡ ይህ የህፃናት ችሎት ለረጅም ጊዜ በአንድ ምድብ ማለትም በልደታ ምድብ ችሎት ብቻ ሲታይ የነበረ ቢሆንም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ግን በሁሉም ምድብ ችሎቶች ለማደራጀት ከፍተኛ ስራ እየተሰራ ይገኛል፡፡

የፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የመዝገብ አፈጻጸም ማደጉ ተገለጸ፡፡

37

ይህ የተገለፀው የፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የ2015 በጀት ዓመት የግማሽ ዓመት የእቅድ አፈፃፀም ውይይቱን በገመገመበት ወቅት ነው፡፡ የውይይት ግምገማው የካቲት 01/2015 ዓ.ም በኢንተር ሌግዠሪ ሆቴል  ተካሂዷል፡፡ በግምገማው የዳኝነት ነፃነት፣ ገለልተኛነት፣ ግልጽነት እና ተጠያቂነት፣ የዳኝነት ቅልጥፍና እና ጥራት እንዲሁም ተደራሽነት ላይ ፍርድ ቤቱ ያለበት ሁኔታ ቀርቦ ውይይት ተካሂዶበታል፡፡ ውይይቱ በዋናነት የስድስት ወር አፈፃፀም በመገምገም የነበሩ ጠንካራ እና ደካማ ጎኖችን ለይቶ ለሚቀጥለው ግማሽ በጀት ዓመት ጠንከራ የስራ መንፈስ ለመገንባት ሲሆን በውይይቱም የፍርድ ቤቱ የበላይ አመራር፣ ተጠሪ ዳኞች፣ ዳይሬክተሮች እና ቡድን መሪዎች ተሳፈዋል፡፡

በኤሌግትሮኒክስ ግዥ (E-GP) ስርዓት ላይ ሲሰጥ የነበረው ስልጠና ተጠናቀቀ፡፡

59

የፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የዳኝነት ስርዓቱን አዘምኖ ቀልጠፋ፣ ተገማች እና ፍትሐዊ የዳኝት ስራን በማከናወን የህዝብን አመኔታ የታረፈ የዳኝነት ተቋም ለመሆን ከፍተኛ ስራ እየሰራ ይገኛል፡፡

በጉዳዮች ፍሰት አስተዳደር እና በፍርድ ቤት መር አስማሚነት መመሪያ ላይ ስልጠና እየተሰጠ ነው፡፡

106

የፌዴራል ፍርድ ቤቶች ትልቅ የለውጥ አካል አድርገው ከሚንቀሳቀሱባቸው እና ተጨባጭ ለውጥ ካስመዘገቡባቸው ጉዳዮች የፍታብሔር የጉዳዮች ፍሰት አስተዳደር (Case Flow Management) መመሪያ ቁጥር 008/2013 እና የፍርድ ቤት መር አስማሚነት (Court Annexed Mediation) መመሪያ ቁጥር 12/2014 ተጠቃሾች ናቸው፡፡

ልጁን የደፈረው ግለሰብ በእስራት ተቀጣ፡፡

206

ዐቃቢ ህግ በተከሳሽ ላይ ያቀረበው በህፃናት ልጆች ላይ እና በዘመዳሞች መካከል በሚደረግ የግብረ ስጋ ድፍረት ወንጅል ክስ ነው፡፡  አቃቢ ህግ ክሱን ግንቦት 14 ቀን 2014 ዓ.ም በቁጥር አቃ/ቃ/ቅ/01495/14 አሻሽሎ አቅርቧል፡፡ በክሱም ሁለት ፍሬ ነገሮች ተብራርተው ቀርበዋል፡፡ እነሱም አንደኛው በኢፌዴሪ የወንጀል ህግ አንቀጽ 627(4)(ሀ) የተመለከተውን የወንጀል ህግ መተላለፍ ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ በኢፌዴሪ የወንጀል ህግ አንቀጽ 654 የተመለከተውን በመተላለፍ  ከእርሱ ጋር ተቃራኒ ፆታ ካላት እድሜዋ 10 (አስር) ዓመት የሆናት እና ልጁ  የሆነችውን የግል ተበዳይ መድፈር የሚል ወንጀል ክስ ነው፡፡

የፍትህ ተቋማት የሰብዓዊ መብቶች ቀን በጥምረት አከበሩ፡፡

70

የፌዴራል የፍትህ ተቋማት ጥምረት የሰብአዊ መብቶችን ቀን በደመቀ መልኩ በፓናል ውይይት አከብረዋል፡፡ የፌዴራል የፍትህ ተቋማት ማለትም የፌዴራል ፍርድ ቤቶች፣ የፍትህ ሚኒስቴር፣ የፌዴራል ፖሊስ፣ የፌዴራል ማረሚያ ቤቶች እና የአዲስ አበባ ፖሊስ በአንድነት የሰብአዊ መብቶችን ቀን በሀገራችን ለአራተኛ ጊዜ ህዳር 29/2015 ዓ.ም በሀይሌ ግራንድ ሆቴል- አዲስ አበባ በፓናል ውይይት አክብረዋል፡፡

በንቃተ ህግና በሴቶች መብቶች ዙሪያ ሲሰጥ ነበረው ስልጠና ተጠናቀቀ፡፡

100

ፌዴራል ፍርድ ቤቶች የዳኝነት ተደራሽነትን፣ ተገማች ፍርድን፣ ቀልጣፋ የዳኝነት ስርዓትን ተቋማዊ ባህል በማድረግ  የህዝብ አመኔታን ያተረፈ የዳኝነት ተቋም ለመገንባት ክፍተኛ ስራ እያከናወኑ ይገኛሉ፡፡ ከነዚህ ስራዎች አንዱ የሰራተኞችን ሁለንተናዊ አቅም ለመገንባት የሚሰጥ ስልጠና ይገኝበታል፡፡

የፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በሙያዊ ስነ-ምግባር እና በችሎት ስርዓት መመሪያ 13/2014 ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጠ፡፡

99

የፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የዳኞችናና የአስተዳደር ሰራተኞች አቅም ለማሳደግ በርካታ ስልጠናዎችን እየሰጠ ይገኛል፡፡ ፍርድ ቤቱ በሙያዊ ስነ-ምግባር እና በችሎት ስርዓት መመሪያ 13/2014 ላይ ለአስተዳደር ሰራተኞች ህዳር 15/03/2015 ዓ.ም በዋና መስሪያ ቤቱ- ልደታ የስልጠና እና የመሰብሰቢያ አዳራሽ ስልጠና ሰጥቷል፡፡  

12