የ2018 ዕቅድ ÷ የሩብ ዓመት አፈፃፀም÷ የላቀ አፈፃፀም ላስመዘገቡ ዳኞች÷ ምድብ ችሎቶች÷ ባለሙያዎች÷በጡረታ ለተለዩ ዕውቅናና ምስጋና ስነ ስርዓት ተካሄደ---------------------------------------------------------
የፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የህግና ፍትህ ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ አቶ ኢሳ ቦሩ÷የቋሚ ኮሚቴው አባላት ፣የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዝደንት ክብርት ወ/ሮ ሌሊሴ ደሳለኝ፣የዳኞች አስተዳደር ጉባኤ አባላት፥ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ሚኒስቴር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ ሂክማ ኸይረዲን÷ የፌደራል የማረሚያ ቤት ኮሚሽን ኮሚሽነር ጄነራል የኑስ ÷ የፌደራል የጠበቆች ማህበር ፕሬዚደንት አቶ ቴዎድሮስ ጌታቸው÷ ክቡራን ተጠሪ ዳኞች፣ ክቡራን ዳኞች፣ ሬጅስትራሮች፣ ዳይሬክተሮች፣ ረዳት ዳኞች በተገኙበት በሸራተን አዲስ ሆቴል የፍርድ ቤቱ የ2018 ዕቅድ እና የሩብ ዓመት አፈፃፀም ቀርቧል::
መክፈቻ በማድረግ የጀመሩት የፍርድ ቤቱ ፕሬዝዳንት ክቡር አቶ ፉአድ ኪያር ፍርድ ቤቱ በ2017 ዓ.ም ውጤታማ የዳኝነት አገልግሎት የሰጠ መሆኑን በየደረጃው ሲካሄዱ የነበሩ የተገልጋይ እርካታ ጥናት÷ የዳኞች ምዘና ውጤት እና ግምገማዎች የሚያመለክቱ መሆኑን ገልጸው ለዚህም የፍርድ ቤቱ ክቡራን ዳኞች፣ ተጠሪ ዳኞች፣ የጉባኤ ተሻሚዎች እና የፍርድ ቤቱ ሰራተኞች ለነበራቸው አስተዋጽኦ ምስጋና በማቅረብ በቀጣይ በጀት ዓመት የጉዳዮች ፍሰት አስተዳደር መመሪያን በጥበቅ መተግበር፣ የፍርድ ቤት መር አስማሚነት ይበልጥ ማከናወን፣ የተገልጋይ እርካታ ጥናት በውስንነት በተነሱ በዳኝነት ጥራት÷ ስነምግባር ÷ ተገማችነት ላይ እየተነሱ የሚገኙ ቅሬታዎች መቀነስ ላይ ትኩረት ማድረግ የሚገባ መሆኑን አቅጣጫ አስቀምጠዋል፡፡
የፍርድ ቤቱ የ 2018 በጀት ዓመት እቅድ እንዲሁም የመጀመሪያው ሩብ ዓመት እቅድ አፈፃፀም በፍርድ ቤቱ ምክትል ፕሬዝዳንት ክብርት ወ/ሮ አሸነፈች አበበ ቀርቧል::