4 ነጥብ 6 ኪሎ ግራም ወርቅ በህገ ወጥ መንገድ ሲሸጥ የተያዘ ግለሰብ በእስራት ተቀጣ

48

የፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 14ኛ ወንጀል ችሎት ግምቱ 38 ሚሊየን ብር የሆነ 4 ነጥብ 6 ኪሎ ግራም ወርቅ በህገ ወጥ መንገድ ሲሸጥ የተያዘው ግለሰብ በእስራት እና በገንዘብ እንዲቀጣ ወሰነ።

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል አሶሳ ዞን ሆሞሻ ወረዳ ነዋሪ የሆነው መሀመድ ሳሊህ መሀመድ ላይ ክስ የመሰረተው በፍትህ ሚኒስቴር የኢኮኖሚ ወንጀል ጉዳዮች ዐቃቤ ሕግ ነው።

ዐቃቤ ሕግ ባቀረበው ክስ ግለሰቡ ሐምሌ 2 ቀን 2016 ዓ.ም ከቀኑ በግምት 6 ሰዓት ሲሆን በአሶሳ ከተማ ልዩ ስሙ አሶሳ ዩኒቨርሲቲ ተብሎ ከሚጠራው ቦታ በተደረገ ክትትል በተሰጠው የወርቅ አቅራቢነት ፍቃድ ብሔራዊ ባንክ ፍቃድ ለሰጣቸው አካላት ብቻ ወርቁን መሸጥ ሲገባዉ በባንክ ፍቃድ ላልተሰጠው አካል ወርቅ ለማስተላለፍ ሲሞክር እጅ ከፍንጅ ተይዟል፡፡

አዲስ በወጡ መመሪያዎች ላይ ገለፃ እና የእቅድ ውል ስምምነት ተካሄደ

52

የፀደቁ መመሪያዎችን በአግባቡ መተግበር እንደሚገባም ተገለፀ።

የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አዲስ በፀደቁ መመሪያዎች በአግባቡ እንዴት መተግበር እንዳለባቸው እና የ2018 በጀት ዓመት እቅድ አፈፃፀም የውል ስምምነት ሰነድን አስመልክቶ ከየምድብ ችሎቶቹ ተጠሪ ዳኞች፣ ዋና ሬጅስትራር፣ ዳይሬክተሮች፣ የስራ ክፍል ኃላፊዎች እና የቡድን መሪዎች ጋር ጥቅምት 25 ቀን 2018 ዓ.ም ልደታ በሚገኘው የዋናው መስሪያ ቤት መሰብሰቢያ አዳራሽ ውይይት ተደረገ።

በእለቱ በነበረ መርሃ-ግብር የተከበሩ ፉአድ ኪያር የፍርድ ቤቱ ፕሬዝዳንት በእንኳን ደህና መጣችሁ መልእክታቸው ወቅት መመሪያ ላይ ተንተርሶ አሰራርን ወጥ ለማድረግ ፤ በውል ስምምነት መሠረት ስራን ቆጥሮ ለመቀበል እና ለመመለስ፤ እንዲሁም ሌሎች መነሳት በሚገባቸው ነገሮች ላይ ለመወያየት መድረኩ መመቻቸቱን ተናግረው መርሃግብሩን አስጀምረዋል።

የሴቶችና ህፃናት የወንጀል ችሎት የዳኞች ፎረም የ2018 የመጀመሪያው ውይይትና ስልጠና በቢሾፍቱ እየተካሄደ ይገኛል

82

የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የሴቶችና ህፃናት የወንጀል ችሎት የዳኞች ፎረም የ2018 የመጀመሪያው ውይይትና ስልጠና በቢሾፍቱ እየተካሄደ ይገኛል::

የስልጠናው እና የውይይቱን መክፈቻ ያደረጉት የፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ምክትል ፕሬዚደንት ክብርት ወ/ሮ አሸነፈች አበበ ሲሆኑ የዳኞች እርስ በርስ ውይይት እና በመረጧቸው ርዕሰ ጉዳዮች ስልጠና መካሄዱ ተቀራራቢ የህግ አተረጓጎምና አሰራር እንዲኖር÷ ልምድና ክህሎት በማዳበር ቀልጣፋና ጥራት ያለው ዳኝነት ለመስጠት አስተዋፅዖ እንዳለው በመግለፅ በሀገር አቀፍና ሀገራችን ባፀደቀቻቸው ልዩ የሴቶችና ህፃናት ህጐች ውይይት እና ስልጠና መካሄዱ ዳኝነት ፈልገው የሚቀርቡ ሴቶችና ህፃናት መብታቸው እንዲረጋገጥ ጉልህ አስተዋፅዖ እንዳለው ገልፀዋል::

ከድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር የወሳኝ ሁነቶች ምዝገባና የነዋሪዎች መረጃ ኤጀንሲ ጋር የመግባቢያ ስምምነት ተደረገ

73

የፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ከድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር የወሳኝ ሁነቶች ምዝገባና የነዋሪዎች መረጃ ኤጀንሲ ጋር የመግባቢያ ስምምነት በድሬዳዋ ከተማ ተፈረመ፡፡ ስምምነቱ በፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ድሬዳዋ ምድብ ችሎት የሚሰጡ የፍቺ እና የጉዲፈቻ ውሳኔዎች በፍርድ ቤቱ በሚዘጋጁ ማዕከላት የምዝገባ አገልግሎቶችን ባለጉዳዮች እንዲያገኙ የሚያስችል ሲሆን በዚህም የተገልጋዮችን ጊዜ እና ገንዘብ በመቆጠብ መጉላላትን የሚያስቀር ይሆናል፡፡

የድሬዳዋ ምድብ ችሎት የ2018 የሩብ ዓመት አፈፃፀም እና የዕውቅናና ምስጋና መርሀ ግብር ተካሄደ--

98

የፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አመራሮች÷ ክቡራን ዳኞች፣ ሬጅስትራሮች፣ ዳይሬክተሮች፣ ረዳት ዳኞች÷ ሰራተኞች በተገኙበት በድሬዳዋ ከተማ የፍርድ ቤቱ የ2018 ዕቅድ እና የሩብ ዓመት አፈፃፀም በፍርድ ቤቱ ምክትል ፕሬዝዳንት ክብርት ወ/ሮ አሸነፈች አበበ ቀርቧል:: እንዲሁም የድሬዳዋ ምድብ ችሎት የሩብ ዓመት አፈፃፀም በምድብ ችሎቱ ተጠሪ ዳኛ ደመቀ መኮንን ቀርቧል::

የ2018 ዕቅድ ÷ የሩብ ዓመት አፈፃፀም÷ የላቀ አፈፃፀም ላስመዘገቡ ዳኞች÷ ምድብ ችሎቶች÷ ባለሙያዎች÷በጡረታ ለተለዩ ዕውቅናና ምስጋና ስነ ስርዓት ተካሄደ---------------------------------------------------------

97

የ2018 ዕቅድ ÷ የሩብ ዓመት አፈፃፀም÷ የላቀ አፈፃፀም ላስመዘገቡ ዳኞች÷ ምድብ ችሎቶች÷ ባለሙያዎች÷በጡረታ ለተለዩ ዕውቅናና ምስጋና ስነ ስርዓት ተካሄደ---------------------------------------------------------

የፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የህግና ፍትህ ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ አቶ ኢሳ ቦሩ÷የቋሚ ኮሚቴው አባላት ፣የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዝደንት ክብርት ወ/ሮ ሌሊሴ ደሳለኝ፣የዳኞች አስተዳደር ጉባኤ አባላት፥ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ሚኒስቴር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ ሂክማ ኸይረዲን÷ የፌደራል የማረሚያ ቤት ኮሚሽን ኮሚሽነር ጄነራል የኑስ ÷ የፌደራል የጠበቆች ማህበር ፕሬዚደንት አቶ ቴዎድሮስ ጌታቸው÷ ክቡራን ተጠሪ ዳኞች፣ ክቡራን ዳኞች፣ ሬጅስትራሮች፣ ዳይሬክተሮች፣ ረዳት ዳኞች በተገኙበት በሸራተን አዲስ ሆቴል የፍርድ ቤቱ የ2018 ዕቅድ እና የሩብ ዓመት አፈፃፀም ቀርቧል::

መክፈቻ በማድረግ የጀመሩት የፍርድ ቤቱ ፕሬዝዳንት ክቡር አቶ ፉአድ ኪያር ፍርድ ቤቱ በ2017 ዓ.ም ውጤታማ የዳኝነት አገልግሎት የሰጠ መሆኑን በየደረጃው ሲካሄዱ የነበሩ የተገልጋይ እርካታ ጥናት÷ የዳኞች ምዘና ውጤት እና ግምገማዎች የሚያመለክቱ መሆኑን ገልጸው ለዚህም የፍርድ ቤቱ ክቡራን ዳኞች፣ ተጠሪ ዳኞች፣ የጉባኤ ተሻሚዎች እና የፍርድ ቤቱ ሰራተኞች ለነበራቸው አስተዋጽኦ ምስጋና በማቅረብ በቀጣይ በጀት ዓመት የጉዳዮች ፍሰት አስተዳደር መመሪያን በጥበቅ መተግበር፣ የፍርድ ቤት መር አስማሚነት ይበልጥ ማከናወን፣ የተገልጋይ እርካታ ጥናት በውስንነት በተነሱ በዳኝነት ጥራት÷ ስነምግባር ÷ ተገማችነት ላይ እየተነሱ የሚገኙ ቅሬታዎች መቀነስ ላይ ትኩረት ማድረግ የሚገባ መሆኑን አቅጣጫ አስቀምጠዋል፡፡

የፍርድ ቤቱ የ 2018 በጀት ዓመት እቅድ እንዲሁም የመጀመሪያው ሩብ ዓመት እቅድ አፈፃፀም በፍርድ ቤቱ ምክትል ፕሬዝዳንት ክብርት ወ/ሮ አሸነፈች አበበ ቀርቧል::

የሰንደቀ ዓላማ ቀን እና የችሎት መክፈቻ መርሃ-ግብር ተከናወነ፡፡

105

በኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፓብሊክ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የሰንደቅ ዓላማ ቀን እና የችሎት መክፈቻ መርሃ ግብር በደማቅ ስነ-ስርዓት ጥቅምት 3 ቀን 2018 ዓ.ም በዋናው መስሪያ ቤት እና ልደታ ምድብ ችሎት ተከናወነ፡፡በኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፓብሊክ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የሰንደቅ ዓላማ ቀን እና የችሎት መክፈቻ መርሃ ግብር በደማቅ ስነ-ስርዓት ጥቅምት 3 ቀን 2018 ዓ.ም በዋናው መስሪያ ቤት እና ልደታ ምድብ ችሎት ተከናወነ፡፡

የፌ/መ/ደ/ፍርድ ቤት ዓመታዊ የአስተዳደር ሰራተኞች በዓል እና የችሎት መክፈቻ በደማቅ ሁኔታ ተከበረ

102

የፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የአስተዳደር ሰራተኞች ዓመታዊ በዓል እና የችሎት መክፈቻ ከአንድ ሺህ በላይ ሰራተኞች፥ ክቡራን ፕሬዝዳንቶች፥ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባልና የፌደራል ፍርድ ቤቶች የሠው ሀብት ስራ አመራር ጉባዔ አባላት ክብርት ወ/ሮ ከዲጃ ያሲን እና ክቡር ዶ/ር ከበደ ገነቴ÷ አስተባባሪ ሬጅስትራሮች ፣ ዳይሬክተሮች ÷ ሬጅስትራሮች እና የስራ ክፍል ኃላፊዋች በተገኙበት በፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ዋና መስሪያ ቤት ግቢ ጥቅምት 1/2018 ዓ.ም እየተከበረ ይገኛል።

የአቃቂ ቃሊቲ እና የንፋስ ስልክ ምድብ ችሎቶች የስራ ጉብኝት ተካሄደ::

169

የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ምክትል ፕሬዚደንት ክብርት ወ/ሮ አበባ እምቢአለ÷የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ምክትል ፕሬዚደንት ክብርት ወ/ሮ አሸነፈች አበበ እንዲሁም ሌሎች የፍርድ ቤቱ አመራሮች በተገኙበት በፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አቃቂ ቃሊቲ እንዲሁም ንፋስ ስልክ ምድብ ችሎቶች አጠቃላይ የስራ አፈፃፀም በተለይም ከቴክኖሎጂ ትግበራ ዝግጁነት አንፃር ጉብኝት የተከናወነ ሲሆን በሁለቱ ምድብ ችሎቶች ሙሉ ዲጂታላይዝ ለማድረግና ወደ ሌሎች ለማስፋፋት በሚያስችል የግብአት÷ የሰው ሀይል÷ የግንዛቤ ማስጨበጥ እንዲሁም የልምድ ልውውጥ ጉዳዮች ላይ ትኩረት በማድረግ በአጭር ቀናት በሁለቱ ምድብ ችሎቶች ሙሉ ትግበራ ስለሚደረግበት ሁኔታ ውይይት ተደርጓል::

ለአስተዳደር ሠራተኞች የበዓል ድጋፍ ( ማዕድ ማጋራት ) ተደረገ ::

158

የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የ2018 አዲስ ዓመት ምክንያት በማድረግ በሁሉም ምድብ ችሎት ለሚገኙ ለ1583 የአስተዳደር ሰራተኞች ድጋፍ አደረገ::

በሴቶች እና ህፃናት ጉዳይ ላይ በጋራ ለመስራት የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ ተፈረመ።

143

የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ከኢ.ፌ.ዲ.ሪ የሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ጋር በሴቶች እና ህፃናት ባጠቃላይ ልዩ ድጋፍ በሚሹ የህብረተሰብ ክፍሎች የተቀላጠፈ፣ ጥራት ያለው ፣ ተደራሽ፣ ውጤታማ የዳኝነት አገልግሎት ለመስጠት ፣ በዳኝነት ሂደት እና በኃላ ለህፃናት እና ሴቶች የተቋማቱ ተቋማዊ ነፃነት በጠበቀ በህግ ማሻሻያዎች፣ በስልጠና፣ በሙያ ፣ግብዓት ፣ ድጋፍ በሚያስፈልጋቸው ሌሎች ብርክት ጉዳዮች ላይ በትብብር ለመስራት ውይይት ተደረጎ ቀጣይ ቅንጅታዊ ስራዎች በተመለከተ የመግባቢያ ስምምነት በኢ.ፌ.ዲ.ሪ የሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ሚኒስትር ክብርት ዶ/ር ኤርጎጌ ተስፋዬ እና የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ፕሬዝደንት ክቡር አቶ ፎዓድ ኪያር ተፈርሟል፡፡

በኘሮግራሙ ላይ የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ምክትል ፕሬዝዳንት ክብርት ወ/ሮ አሸነፈች አበበ የፌ/መ/ደረጃ ፍ/ቤት ከሴቶችና ህፃናት አኳያ ያከናወናቸው፣ ቀጣይ ለመስራት የታቀዱ እንዲሁም የመግባቢያ ስምምነት ይዘት በዝርዝር አቅርበዋል::

የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ክብርት ዶክተር ኤርጎጌ ተስፋዬ ሴቶችና ህፃናት ለተለያዩ ጥቃቶች የሚጋለጡበትና ውስብስብ ለሆኑ ችግሮች የሚዳረጉበት ሁኔታ መኖሩን ገልፀዋል። ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ከፍትህ ተቋማት ጋር በመቀናጀት ሰፉፊ ስራ እየሰሩ መሆኑን ጠቁመዋል።

የአመራሮች ስልጠና ተጠናቀቀ::

140

በአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ለተከታታይ 3 ቀናት ለፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አመራሮች ሲሰጥ የነበረው ስልጠና ተጠናቀቀ:: "የፍትህ አካላት ሚና በሀገረ መንግስት ግንባታ" በሚል ርዕስ የተጀመረው ስልጠና በመቀጠል በፍትህ አካላት አመራር ክህሎት ÷ Leadership Style÷ Growth mindset and emotional Intelligence በሚሉ ርዕሶች ስልጠናው ተሰጥቷል::

አጠቃላይ የጤና ምርመራ በነፃ ለዳኞች

139

የፌደራል የመ/ደ/ፍ/ቤት ከኢ.ፌ.ድሪ የጤናሚኒስቴር ጋር በመተባበር ለፌደራል ፍ/ቤት ዳኞች እና ቤተሰቦቻቸዉ ነፃ አጠቃላይ የጤና ምርመራበመስጠት ላይ ይገኛል፡፡

ፍ/ቤቱ ከኢ.ፌ.ድ.ሪ የጤና ሚኒስቴር የኮተቤ ኤካ ሆስፒታል ጋር በመነጋገር በዳኞች የመኖሪያ ግቢ አፖርታማ ግዚያዊ የምርመራ ክሊኒክ እና ላብራቶሪ በማቋቋም ከነሀኔ 19-21/2017 የሚቆይ ነፃ ሕክምና በመስጠት ላይ ይገኛል፡፡ በሦስት ቀናት የሚሰጡትሕክምና አገልግሎቶች የጠቅላላ ምርመራ፣የአይንህክምና፣የልብ ምርመራ እና አልትራ ሳውንድ፣የማህፀን ፅንስ ምርመራ፣የሕፃናት ሕክምና፣የቆዳሕክምና፣ላብራቶሪ፣ ቀላል ቀዶ ጥገና እና የጤና መረጃ እና ሌሎች ተያያዥ ሕክምናዎች ናቸዉ፡፡

የፌ/መ/ደ/ፍ/ቤት ዋና መ/ቤት ሊያስገነባ ያሰበው ሕንፃ የመጀመሪያ ዲዛይን ለውይይት ቀረበ::

159

የፌ/መ/ደ/ፍ/ቤት ዋና መ/ቤት ሕንፃ ለማስገንባት ከኢትዬጰያ ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን ጋር በግንቦት ወር የሕንፃውን ዲዛይን አፈር ምርመራ እና ውል አስተተዳደር ስራዎችን ለማከናወን ውል መገባቱ ይታወሳል፡፡

የስፖርት ማዘውተሪያ (ጂም)÷ ስቲም÷ሳውና ባዝ÷ የውስጥና የውጪ ህንፃ እድሳት÷ መሰብሰቢያ አዳራሽ ስራ ተጠናቆ ተመረቀ::

181

የፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ዋና መስሪያ ቤት እና የልደታ ምድብ ችሎት የስፖርት ማዘውተሪያ (ጂም)÷ ስቲም÷ሳውና ባዝ ÷የውጪና የውስጥ ህንፃ እድሳት÷ መሰብሰቢያ አዳራሽ ስራ ተጠናቆ የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዚደንት ክብርት ወ/ሮ ሌሊሴ ደሳለኝ÷ የሕግና ፍትሕ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ክቡር አምባሳደር ደግፌ ቡላ፣የፌደራል የዳኞች አስተዳደር ጉባዔ አባላት÷ የፌደራል ጠበቆች ማህበር ፕሬዚደንት ክቡር አቶ ቴዎድሮስ ጌታቸው÷ የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ፕሬዚደንት÷ የበላይ ሀላፊዎች÷ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚደንትና ምክትል ፕሬዚደንት ፅ/ቤት ሀላፊዎች÷ የፌዴራል ፍርድ ቤቶች ሀላፊዎች÷ ተጠሪ ዳኞች÷ ክቡራን ዳኞች÷ ዋናና አስተባባሪ ሬጅስትራሮች÷ ዳይሬክተሮች ÷ ባለሙያዎች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት በተገኙበት የምረቃ መርሀ ግብር ተካሂዷል::

1234