በሀረር ከተማ የስራ እና የተለያዩ ቦታዎች ጉብኝት ተደረገ፡፡

99

የፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አመራሮች ፣ ተጠሪ ዳኞች፣ ዳኞች፣ ዳይሬክተሮች የመቻቻል እና የፍቅር ከተማ በሆነችው በሀረር ከተማ በመገኘት በሀረር ከተማ ውስጥ የሚገኙ ከ1300 ዓመታት በላይ እድሜ ያስቆጠሩ የተለያዩ የታሪክ እና የስልጣኔ ምስክር የሆኑ ቅርሶችን እና የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤትን ጎብኝተዋል፡፡ ሀረር ሀገራችን የብዙ ዘመናት ታሪክ እና ስልጣኔ ባለቤት መሆናን ከሚያመለክቱ ቦታዎች አንዱ ሲሆን ጉብኝቱም ስለ ሀረር በቂ ግንዛቤ ለመያዝ የሚያስችል እድል የፈጠረ ነው፡፡

የዳኞች መኖሪያ ቤት ርክክብ እና የድሬዳዋ ምድብ ችሎት የስራ ጉብኝት ተካሄደ::

96

የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት ክቡር አቶ ፋዓድ ኪያር÷ ምክትል ፕሬዚዳንቶች ÷ ተጠሪ ዳኞች እንዲሁም ዳይሬክተሮች በተገኙበት የድሬዳዋ ምድብ ችሎት የዳኝነት አገልግሎት አሰጣጥ የስራ ጉብኝት የተከናወነ ሲሆን በመቀጠልም በፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ድሬዳዋ ምድብ ችሎት ተመድበው የዳኝነት አገልግሎት ለሚሰጡ ክቡራን ዳኞች ከድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር በልዮ ሁኔታ ያለ ዕጣ የተሰጡ እና በፍርድ ቤት ሙሉ ክፍያ እና እድሳት የተደረገባቸው የዳኞች መኖሪያ ቤቶች የድሬዳዋ አስተዳደር የቤቶች ልማት እና የኮንስትራክሽን ቢሮ ሀላፊ ክቡር ኢንጅነር አቶ ዑመር ዱአሌ በተገኙበት የርክክብ መርሀ ግብር ተከናውኗል::

የ2017 የ6ወር የዕቅድ አፈፃፀም ውይይት መድረክ በድሬዳዋ ተካሄደ፡፡

110

የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ፕሬዚደንት ክቡር አቶ ፉዓድ ኪያር፣ ምክትል ፕሬዚዳንቶች÷ የሁሉም ምድብ ችሎቶች ተጠሪ ዳኞች፣ ዳይሬክተሮች እና ሬጅስትራሮች በተገኙበት የፍርድ ቤቱ የ2017 በጀት የ6ወር ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ በድሬዳዋ ተካሂዷል።

አዲስ ለተሾሙ ሬጂስትራሮች የትውውቅና የስራ ገለጻ ተደረገ ፡፡

35

የፌደራል ዳኞች አስተዳደር ጉባኤ አዲስ ለሾማቸው ከ42 በላይ ለሚሆኑ የፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ሬጂስትራሮች የፌደራል መጀመሪያ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ፤ምክትል ፕሬዝዳንት እና የሚመለከታቸው የስራ ክፍል ሃላፊዎች በተገኙበት ዛሬ ማለትም ጥር 08/2017 ዓ.ም በፍርድ ቤቱ መሰብሰቢያ አዳራሽ የስራ ገለጻ ተደርጓል፡፡

ለፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ችሎት ፀኃፊዎች እና ሬጅስትራሮች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ

132

ለፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የጉድፍቻና ፍቺ ምዝገባ ለሚያከናውኑ የችሎት ፀሃፊዎችና ሪጅስትራሮች በወሳኝ ኩነት ምንነት÷በአዲስ አበባ ከተማ በሚገኙ 11 የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤቶች በከተማዋ የሚከሰቱ የጉድፈቻና የፍች ኩነቶች የችሎት ውሳኔ በፍርድ ቤቶች መመዝገብ አስፈላጊነት ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጥቷል፡፡

የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የሴቶችና ህፃናት ችሎት ዳኞች ልምድ ልውውጥ እና የሴቶችና ህፃናት ችሎት የዳኞች ፎረም ምስረታ ተከናወነ;

171

በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የህፃናት ፍትህ ፕሮጀክት ዳይሬክቶሬት ለፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የሴቶችና ህፃናት ችሎት እንዲሁም ጥፋት ነክ ነገር ውስጥ ገብተው የተገኙ ህፃናት ችሎት ዳኞች የልምድ ልውውጥ ውይይት ፕሮግራም በቢሾፍቱ ከተማ ያከናወነ ሲሆን በህፃናት መብት ጥበቃ ላይ ለውይይት መነሻ ፅሁፍ በክቡር ዳኛ ልዑለስላሴ ሊበን ቀርቧል::

ሀገር አቀፍ የዳኝነትና የፍትሕ አካላት የምክክር መድረክ በአርባምንጭ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል።

150

የፌዴራል ፍርድ ቤቶች ፕሬዝዳንቶችና ምክትል ፕሬዝዳንቶች ፣ የፍትሕ ሚኒስቴር ሚኒስትርና ሚኒስትር ዲኤታዎች፣ የፌዴራል ፣ የክልልና የከተማ መስተዳደሮች የዳኝነት አካላት እና የፍትሕ አካላት አመራሮች በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ።

ፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የጉዲፈቻ እና ፍቺ ውሳኔ ምዝገባ ዛሬ ተጀመረ

111

በፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የሚወሰኑ የፍቺ እና ጉዲፈቻ ውሳኔዎችን የመመዝገብ አገልግሎት በአንድ ማዕከል ለመስጠት የሚያስችለውን የስራ ስምምነት ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳዳር የሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ ጋር በፈፀመው መሰረት ዛሬ ታህሳስ 9/2017 ዓ.ም በይፋ አገልግሎቱ በፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በአራዳ÷ የካ እና ቦሌ ምድብ ችሎቶች ተጀምሯል።

በፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የፍቺ እና የጉዲፈቻ ውሳኔዎች ምዝገባ ተጀመረ፡፡

159

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳዳር የሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ በፍርድ ቤት የሚወሰኑ የፍቺ እና ጉዲፈቻ ውሳኔዎችን የመመዝገብ አገልግሎት በአንድ ማዕከል ለመስጠት የሚያስችለውን የስራ ስምምነት ከፌደራል የመጀመርያ ደረጃ ፍርድ ቤት ጋር ቀደም ብሎ ስምምነት መፈጸሙ ይታወቃል፡፡ በስምምነቱ መሰረትም ዛሬ ታህሳስ 9/2017 ዓ.ም በይፋ አገልግሎቱን በአራዳ እና ቦሌ ምድብ ችሎቶች መስጠት ጀምሯል።

የቤተሰብ ችሎት÷ የጉዲፈቻ ችሎት÷ ተጠሪ ዳኞች እና አስተባባሪ ሬጅስትራሮች በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳዳር የሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ በመገኘት ጉብኝት እና ስልጠና ተከናወነ

173

የፌደራል የመጀመርያ ደረጃ ፍርድ ቤት አመራሮች እና የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳዳር የሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር አቶ ዮናስ አለማየሁ በተገኙበት በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳዳር የሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ የቴክኖሎጂና የሪፎርም ተግባራት ጉብኝት ተካሂዷል::

የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አመራሮች እና ዳኞች አድዋ ዜሮ ሙዚየም፣ "ለነገዋ" የሴቶች ተሃድሶ እና የክህሎት ማበልፀጊያ ማዕከል እንዲሁም የአይነ ብርሃን አዳሪ ትምህርት ቤት ጉብኝት አደረጉ

149

የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አመራሮች እና ዳኞች በአዲስ አበባ ከተማ በአጭር ጊዜ ውስጥ ተሰርተው ወደ ተግባር የገቡ ፕሮጀክቶች ውስጥ የአድዋ ዜሮ ዜሮ ሙዚየም÷ "ለነገዋ" የሴቶች ተሃድሶ እና የክህሎት ማበልፀጊያ ማዕከል እንዲሁም ብርሀን የአይነ ሰውራን 2ተኛ ደረጃ አዳሪ ትምህርት ቤትን ህዳር 28/2017 ዓ.ም ጎብኝተዋል።

የክርክር አመራር እና ዕግድ አሰጣጥ ላይ የውይይት መድረክ ተካሄደ

160

የፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ዳኞች በተገኙበት የክርክር አመራር እና ዕግድ አሰጣጥ በሚመለከት በአደዋ ሙዚየም የውይይት መድረክ ተካሄደ፡፡

የቻይና ብሔራዊ የዳኝነት ኮሌጅ ልዑካን ፍርድ ቤቱን ጎበኙ::

139

በቻይና ብሔራዊ የዳኝነት ኮሌጅ ምክትል ፕሬዝዳንት እና የዓለም አቀፍ ግንኙነት ዳይሬክተር ዶ/ር ዋንግ ጂያፈን የተመራ ልዑክ ቡድን የፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤትን ጎበኙ፡፡

1234