የፌዴራል ፍርድ ቤቶች አንድ የለውጥ አካል አድርገው እየሰሩባቸው ከሚገኙ ጉዳዮች አንዱ የፍርድ ቤት መር አስማሚነት ነው፡፡ የፍርድ ቤት መር አስማሚነት ለፍርድ ቤቶች ስራዎችን ከማቀላጠፍና ውጤታማ ስራዎችን ከመከወን አንፃር ያለው ሚና የጎላ በመሆኑ በ2014 ዓ.ም መመሪያ (መመሪያ ቁጥር 12/2014) ተዘጋጅቶለት ወደ ስራ ተገብቷል፡፡ ይህን ተከትሎ የፍርድ ቤት መር አስማሚነትን የፌዴራል ፍርድ ቤቶች በሚፈልጉት ልክ ይፈፀም ዘንድ ለዳኞች፣ ለረዳት ዳኞች፣ ለሬጅስትራሮች እና ከስራው ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት ላላቸው ባለሙያዎች የእውቀትና የክህሎት ማሳደጊያ ስልጠናዎችን እየሰጠ ይገኛል፡፡