አዲስ ለተሾሙ ዳኞች አቀባበልና ትዉዉቅ ተደረገ፡፡

4

የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት እጩ ዳኞችን ሹመት በዛሬዉ እለት ባካሄደው 11ኛ መደበኛ ስብሰባ 23 ሴት እጩዎችንና 27 ወንድ እጩዎችን በድምሩ 50 የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት እጩ ዳኞችን ሹመት አጽድቋል፡፡

በድሬደዋ ምድብ ችሎት ጉብኝት እና የ6 ወራት የእቅድ አፈፃፀም ግምገማ ተካሄደ።

31

የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ጥር 21 ቀን 2018 . በድሬደዋ ከምድብ ችሎቱ ዳኞች፣ የክፍል ኃላፊዎች፣ የቡድን መሪዎች እና ሁሉም<

የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ለዋና መስሪያ ቤት አዲስ በሚያሰራው ህንፃ ዲዛይን ላይ ከባለ ድርሻ አካለት ጋር ምክክር ተደረገ።

28

የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ለዋና መስሪያ ቤት እንዲሁም በኢፌ.ዴ.ሪ ፍትህ ሚኒስቴር ጠቅላይ ዐቃቢ ህግ ዘርፍ የልደታ ቅርንጫፍ ለፅህፈት ቤት በአዲስ የሚገነቡ ህንፃዎች ዲዛይንን አስመልክቶ ከባለ ድርሻ አካላት ጋር ጥር 23 ቀን 2018 ዓ∙ም በካፒታል ሆቴል ምክክር ተደረገ።

አዲስ ለተቀጠሩ ሰራተኞች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ፡፡

59

የፌዴራል መጀመረያ ደረጀ ፍርድ ቤት የጀመረዉን የሪፎርም ስራ ለማሳለጥ እና የዳኝነት አገልግሎቱን ለማሻሻል አዲስ በተጠናው የሰው ሃይል መዋቅር መሰረት በርካታ የሰው ኃይል እየቀጠረ ይገኛል። በዚሁ መሰረት ባለፉት ስድስት ወራት ፍርድ ቤቱን የተቀላቀሉ ከአንደ መቶ ዘጠና በላይ ለሚሆኑ እና በተለያዩ የስራ መደቦች ላይ ለተቀጠሩ ሰራተኞች አጠቃላይ የፌደራል ፍርድ ቤቶችን አደረጃጀት እና አሰራር እና ህጎች እንዲሁም ሰራተኞች ሊላበሱ ስለሚገባቸው ሙያዊ ስነ-ምግባርን በተመለከተ በፍርድ ቤቱ የመሰብሰቢያ አደራሽ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጥቷል።

የ6 ወራት የእቅድ አፈፃፀም ግምገማ ተካሄደ።

61

የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት ክቡር አቶ ፉዓድ ኪያር፣ ምክትል ፕሬዚዳንት አሸነፈች አበበ÷ የሁሉም ምድብ ችሎቶች ተጠሪ ዳኞች÷ ዳይሬክተሮች÷ አስተባባሪ ሬጅስትራሮች እና የዳኞች ፎረም ሰብሳቢዎች በተገኙበት የ2018 በጀት ዓመት የ6 ወራት እቅድ አፈፃፀም ግምገማ ተካሂዷል::

የመርሀ ግብሩን መክፈቻ ያደረጉት የፍርድ ቤቱ ምክትል ፕሬዚደንት ወ/ሮ አሸነፈች አበበ ሲሆኑ በ6ወራት በየምድቡና በየዳይሬክቶሬቱ ተገምግሞ ከቀረበው ከመዝገብ አፈፃፀም÷

የፍትሀብሄር ጉዳዮች ፍሰት አስተዳደር መመሪያ በጥብቅ ከመተግበር በተለይም ከጊዜ ገደብ በተጨማሪ ግልፅ ችሎት ማስተናገድ÷ ቅድሚያ ትኩረት የሚሹ ተገልጋዮች[ነፍሰጡር÷ ህፃናት÷ አረጋዉያን÷ አካል ጉዳተኞች÷ ቅድሚያ ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች(ዕግድ÷ እስረኛ ያላቸዉ÷ ሀገራዊ ፋይዳ ያላቸዉ÷ ቀለብ..]÷ ችሎት ሰዓት÷ ስነምግባር ክትትል÷ አስማሚነት ÷ የሬጅስትራር አገልግሎት አሰጣጥ÷ ከጥንታዊ ስራዎች÷ የባለሙያዎች አቅም ከመገንባት አንፃር በርካታ የዳኝነት እና አስተዳደራዊ ተግባራት በዉስን የሰዉ ሀይል በጀት መከናወኑ ይህም ጥንካሬ በበለጠ ቁርጠኝነት ሊጠናከር እንደሚገባ ዉስንነቶች ላይ በቀጣይ ወራት በበለጠ መረባረብ እንደሚያስፈልግ ገልፀዋል::

ሰብዓዊ መብት ከማስከበር አንፃር የዳኞች ሚና በተመለከተ የምክክር መድረክ ተካሄደ::

76

የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ከኢትዮጲያ የሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ጋር በጋራ በመሆን ሰብዓዊ መብት ከማስከበር በተለይም ለጥቃት ተጋላጭ የሆኑ ሴቶች እና ህፃናት መብቶች ከማስከበር አንፃር የዳኞች ሚና በተመለከተ ያሉ መልካም ተሞክሮዎች በዋናነትም በህግ አተገባበር÷ በአሰራር መሻሻል ባለባቸዉ ጉዳዮች ላይ ትኩረት በማድረግ የምክክር መድረክ በቢሾፍቱ ከተማ ለቤተሰብ ችሎት እና በሴቶች እና ህፃናት ልዩ ችሎት ለሚሰሩ ክቡራን ዳኞች ስልጠና እና ምክክር ተካሂዷል::

የስራ ክርክር ችሎቶች አስማሚ ረዳት ዳኞች የልምድ ልውውጥ መድረክ ተከናወነ።

89

የአሰሪና ሰራተኛ ጉዳዮች በፍርድ ቤት መር አስማሚነት ማዕቀፍ ውስጥ እንዲያልፉ በመመሪያ ከተደነገጉ የክርክር አይነቶች አንዱ ሲሆን በፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ካለው አጠቃላይ የስምምነት ውጤት ላይ የማይናቅ ድርሻ አለው፡፡

በኔትዎርክ እና ዳታ ሴንተር አስተዳደር ላይ ስልጠና ተሰጠ ፡፡

30

ለፌዴራል መጀመረያ ደረጃ ፍርድ ቤት ድሬደዋ እና አዲስ አበባ ላሉ ሁሉም ምድብ ችሎት የኔትዎርክ ባለሞያዎች በኔትዎርክ እና ዳታ ሴንተር አስተዳደር ላይ ከታህሳስ 14 እስከ 17 ቀን 2018 ዓ.ም ልደታ በሚገኘው በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የፍርድ አፈፃፀም ፅህፈት ቤት 2ኛ ፎቅ በሚገኘው የስልጠና ማዕከል ስልጠና እየተሰጠ ነው፡፡

በወንጀል ፍትህ አስተዳደር የፍ/ቤቶች (የዳኝነት አካል ) ሚና በሚል ትምህርታዊ ገለፃ ተሰጠ ።

19

ትምህርታዊ ገለፃዉ የተሰጠዉ ለአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የ 3ኛ አመት የህግ ተማሪዎች ሲሆን ገለፃዉን የሰጡት የፌ/መ/ደ/ፍ/ቤት ኘሬዝዳንት ክቡር አቶ ፋአድ ኪያር ናቸዉ።

ለክቡራን ዳኞች ውጤት እየተገለፀ ይገኛል::

123

የ2017 ዓ.ም የዳኞች የሥራ አፈጻጸም ምዘና ተካሄዶ ለክቡራን ዳኞች ውጤቱ እየተገለፀ ይገኛል::

የፌዴራል ዳኞች አስተዳደር ጉባኤ ባወጣው የዳኞች የስራ አፈጻጸም ምዘና መመሪያ ቁጥር 09/2015 መሰረት የፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ዳኞች ከጥቅምት 1/2017 እስከ ሐምሌ 30/2017 ባለው ጊዜ ለ3ኛ ጊዜ የተካሄደው ምዘና ውጤት ለዳኞች የማሳወቅ ተግባር እየተከናወነ ይገኛል፡፡

በመመሪያው መሰረት የዳኞችን የስራ አፈጻጸም 12 አካላቶች የሚመዝኑ ሲሆን እያንዳንዱ መዛኝ የሚሰጠውም ውጤት በመመሪያው ላይ ተደንግጎ ይገኛል፡፡ በዚሁ አግባብ 157 ዳኞች የስራ አፈጻጸማቸው ተመዝኖ የተሰጠ ውጤት በአመራሩ በአካል ሊገለፅ እንደሚገባ በመመሪያው አንቀፅ 21 በሚገልፀዉ መሰረት የ2017 የምዘና ውጤት እንዲሁም የ3 ተከታታይ አመታት ዉጤት ማጠቃለያ በ7 ምድብ ችሎቶች ለሚገኙ ዳኞች ለእያንዳንዱ የማሳወቅ ተግባር ተከናውኗል::

2ኛ ዙር ስልጠና ለችሎት ቅርብ ለሆኑ ባለሙያዎች በሙያዊ ስነ-ምግባር፣ በተግባቦት ክህሎት፣ በአገልግሎት አሰጣጥ እና በተገልጋዮች አያያዝ ላይ እየተሰጠ ይገኛል።

100

በስነ-ምግባር፣ በሙያዊ ስነ-ምግባር፣ በተግባቦት ክህሎት፣ በአገልግሎት አሰጣጥ፣ በተገልጋዮች አያያዝ እና በመልካም አስተዳደር ላይ በፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ

ከችሎት ስራ ጋር ቅርብ ለሆኑ ባለሙያዎች የክህሎት እና የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል። ***********

116

በስነ-ምግባር፣ በሙያዊ ስነ-ምግባር፣ በተግባቦት ክህሎት፣ በአገልግሎት አሰጣጥ፣ በተገልጋዮች አያያዝ እና በመልካም አስተዳደር ላይ በፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አዲስ አበባ ሁሉም ምድብ ችሎቶች ለሚገኙ የችሎት ባለሙያዎች ከአዲስ አበበ ስራ አመራር አካዳሚ ጋር በመተባበር በሲቪል ሰርቪስ ዮኒቨርስቲ ከታህሳስ 6 እስከ 11 ቀን 2018 ዓ.ም በሁለት ዙር ለሶስት ለሶስት ቀናት የሚቆይ ስልጠና በዛሬዉ እለት ተጀምሮል ።

በስልጠናው መክፈቻ ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ክቡር አቶ ፋዓድ ኪያር የፍርድ ቤቱን ስራ በአግባቡ ለመምራት ሁሉንም የፍርድ ቤት አመራሮች እና ሰራተኞች ማብቃት ተገቢ መሆኑን በማመን በሱሉልታ የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ለአመራሮች፣ በልደታ ዋናው መስሪያ ቤት ለረዳት ዳኞች ለሬጅስትራሮች እና ለቡድን መሪዎች ከዚህ በፊት ስልጠና መሰጠቱን በማስታወስ አሁን ደም በሲቪል ሰርቪስ ዮኒቨርስቲ ከአዲስ አበባ ስራ አመራር አካዳሚ ጋር በመተባበር በሁለት ዙር በአዲስ አበባ ሁሉም ምድብ ችሎቶች ለሚሰሩ 600 (ስድስት መቶ) የችሎት ሰራተኞች በሁለት ዙር ለሶስት ቀናት የሚቆይ ስልጠና ታቅዶ እየተሰጠ መሆኑን ገልፀዎል ።

ለረዳት ዳኞች በፍትሀብሄር ስነስርዓት የአቤቱታዎችን የህግ ብቃት መመርመር ÷እግድ ፍርድ አፃፃፍ ላይ ስልጠና መስጠት ተጀመረ።

106

የክስ አቤቱታዎችን በፍትሀብሔር ስነ ስርዓት ህጉ መሰረት ህጋዊ ብቃታቸውን ከመመርመር አንፃር የረዳት ዳኞች ሚና÷ ዕግድ አሰጣጥ እንዲሁም ፍርድ ተጨማሪ ያንብቡ

በፆታዊ ጥቃት መከላከል ፣በህፃናት እድገት እና ተግባቦት የፍርድ ቤት ሚና በተመለከተ ስልጠና ተሰጠ *********

102

የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ከሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ጋር ባደረገው የመግባቢያ ስምምነት መሰረት ለ ሴቶችና ህፃናት የወንጀል ችሎት ዳኞች÷ ለቤተሰብ ችሎት ዳኞች÷ ለማህበራዊ ሳይንስ ባለሙያዎች በህፃናት እድገትና ተግባቦት በዶ/ር እመቤት ሙልጌታ( በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የsocial worker መምህር)÷ በፆታዊ ጥቃት መከላከል የፍርድ ቤት ሚና በተመለከተ ( በአቶ ኖህ ውብሸት (የ psycology and gender አማካሪ) በአዳማ ከተማ ከታህሳስ 3/2018ዓ.ም ጀምሮ ስልጠና ተሰጥቷል::

ስልጠና ለሬጅስትራሮች

153

በስነ-ምግባር፣ በመሪነት፣ በስነ-ስርዓት ህጎች ዓላማ አና መርሆች እንዲሁም በሬጅስትራር አሰራሮች ላይ

በሚስተዋሉ ችግሮች እና መፍትሄዎቻቸው ላይ ለሬጅስትራሮች ስልጠና ተሰጠ።

የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በአዲስ አበባ እና ድሬደዋ ለሚገኙ የሁሉም ምድብ ችሎቶች ሬጅስትራሮች ህዳር 26 እና 27 ቀን 2018 ዓ.ም በዋናው መስሪያ ቤት መሰብሰቢያ አዳራሽ በተቋሙ ከፍተኛ አመራሮች እና ዳኞች አማካኝነት በሬጅስትራር አገልግሎት አሰጣጥ የሚጠበቅ ስነ-ምግባር ፣ ሬጅስትራሮች በዳኝነት ስርዓት ውስጥ ያላቸው የመሪነት ሚናን፣ በስነ-ስርዓት ህግጋት ዓላማ እና መርሆችን ከማሳካት አኳያ የሬጅስትራሮች ሚናን እንዲሁም በዳኝነት ክፍያ አፈፃፀም እና በሬጅስትራር አሰራሮች ላይ የሚስተዋሉ ችግሮች እና መፍትሄዎቻቸው በሚሉ እና በተለዮ ርእሶች ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ እና የማነቃቂያ ስልጠና ተሰጠ።

12345