የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት ክቡር አቶ ፉዓድ ኪያር፣ ምክትል ፕሬዚዳንት አሸነፈች አበበ÷ የሁሉም ምድብ ችሎቶች ተጠሪ ዳኞች÷ ዳይሬክተሮች÷ አስተባባሪ ሬጅስትራሮች እና የዳኞች ፎረም ሰብሳቢዎች በተገኙበት የ2018 በጀት ዓመት የ6 ወራት እቅድ አፈፃፀም ግምገማ ተካሂዷል::
የመርሀ ግብሩን መክፈቻ ያደረጉት የፍርድ ቤቱ ምክትል ፕሬዚደንት ወ/ሮ አሸነፈች አበበ ሲሆኑ በ6ወራት በየምድቡና በየዳይሬክቶሬቱ ተገምግሞ ከቀረበው ከመዝገብ አፈፃፀም÷
የፍትሀብሄር ጉዳዮች ፍሰት አስተዳደር መመሪያ በጥብቅ ከመተግበር በተለይም ከጊዜ ገደብ በተጨማሪ ግልፅ ችሎት ማስተናገድ÷ ቅድሚያ ትኩረት የሚሹ ተገልጋዮች[ነፍሰጡር÷ ህፃናት÷ አረጋዉያን÷ አካል ጉዳተኞች÷ ቅድሚያ ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች(ዕግድ÷ እስረኛ ያላቸዉ÷ ሀገራዊ ፋይዳ ያላቸዉ÷ ቀለብ..]÷ ችሎት ሰዓት÷ ስነምግባር ክትትል÷ አስማሚነት ÷ የሬጅስትራር አገልግሎት አሰጣጥ÷ ከጥንታዊ ስራዎች÷ የባለሙያዎች አቅም ከመገንባት አንፃር በርካታ የዳኝነት እና አስተዳደራዊ ተግባራት በዉስን የሰዉ ሀይል በጀት መከናወኑ ይህም ጥንካሬ በበለጠ ቁርጠኝነት ሊጠናከር እንደሚገባ ዉስንነቶች ላይ በቀጣይ ወራት በበለጠ መረባረብ እንደሚያስፈልግ ገልፀዋል::