የፍርድ ቤት መር አስማሚነትን ከባህል እና ሽምግልና ስርአት እንዲሁም ከሃይማኖት አባቶች ጋር ለማቀናጀት የምክክር መድረክ በድሬደዋ ከተማ ተካሄደ።

19

የፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት እያከናወነ ያለውን የፍርድ ቤት መር አስማሚነት የበለጠ ለማጠናከርና የህብረተሰቡን ተሳትፎ ለማሳደግ ይጠቅም ዘንድ ከድሬደዋ ከተማ ከንቲባ ጽ/ቤት ጋር በመተባበር በከተማ አስተዳደሩ ካሉ የባህል ሽማግሌዎች (አባ ገዳና ኡጋዝ) እንዲሁም ከሃይማኖት አባቶች ጋር የውይይት መድረክ ተዘጋጀ ። በመድረኩም የሀገር ሽማግሌዎችና የሀይማኖት አባቶች ወደ ፍርድ ቤቱ የፍርድ ቤት መር አስማሚነት ትግበራ ሥርዓት በመግባት አገልግሎት የሚሰጡበትና የፍትህ ተደራሽነትን በሚያረጋግጡበት መንገድ ላይ ውይይት ተደርጓል።

ተጫራቾች ተጋብዛችኋል !!

30

የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ለዋና መስሪያ ቤት እና በኢፌ.ዴ.ሪ ፍትህ ሚኒስቴር ጠቅላይ ዐቃቢ ህግ ዘርፍ ለልደታ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት በአዲስ የሚገነቡ ህንፃዎች (2B+G+11 እና 2B+G+6) በተመለከተ የዲዛይን የአፈር ምርምራ እናየማማከር ስራውን በማጠናቀቅ የግንባታ ሂደቱን በግልጽ ጨረታ አውጥቷል፡፡

ዘመናዊ የህጻናት ማስመስከሪያ ክፍል የስራ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ተካሄደ ።

6

‎በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የህጻናት ፍትህ ፕሮጀክት ዳይሬክቶሬት የተሰራ ዘመናዊ የህጻናት ማስመስከሪያ ክፍል (One way mirror) በፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አዲስ ከተማ ምድብ ችሎት በይፋ ስራ ጀምሯል።

ድህረ-ውሣኔ ኦዲት

31

የዳኝነት አገልግሎት ጥራትን ከሚያረጋግጡ ቁልፍ መሳሪያዎች አንዱ ተከታታይነት ያለው የድህረ-ውሣኔ ኦዲት ስራ መስራት ነው፡፡ በተለይም ጥራትን ለማረጋገጥ፣ወጥነት ያለው አሠራርን ለማስፈን፣የስልጠና ፍላጎትን ለመለየት፣ተጠያቂነት እና ግልፅነት ለማስፈን: ክፍተቶችን ለይቶ ለማስተካከል እና የሕዝብ አመኔታ ለማግኘት የድህረ-ኦዲት ውሣኔ አስፈላጊ ነው፡፡

ቅን ኢትዮጵያ ማህበር ለህፃናት ማቆያ አገልግሎት የሚውሉ ቁሳቁሶችን ለፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ድጋፍ አደረገ።

22

ማህበሩ በፍርድ ቤት ለሚገኙ ሰራተኛ እናቶች በስራ ቦታቸው ላይ ሆነው በልጆቻቸው ሁኔታ እንዳይጨናነቁ በቅርበት ልጆቻቸውን እንዲገናኙ በፍርድ ቤቱ ውስጥ የህፃናት ማቆያ መቋቋሙን በማድነቅ የበኩሉን ይህንን ቀና ተግባር ለመደገፍ ለዚህ የህፃናት ማቆያ ድጋፍ ማድረጉን ገልፃል።

በኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ተክኖሎጂ /ICT/ አገልግሎት መገልገያ መሳሪያዎች አያያዝ፣ አስተዳደር እና ጥገና ላይ ያተኮረ የግንዛቤ መሰጨበጫ ሰልጠና እየተሰጠ ነው፡፡

15

የፌዴራል መጀመረያ ደረጃ ፍርድ ቤት የኢንፎርሜሸን እና ኮሙዩኒኬሸን ዳይሬክቶሬት በኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ተክኖሎጂ /ICT/ አገልግሎት መገልገያ መሳሪያዎች አያያዝ፣ አስተዳደር እና ጥገና ላይ ያተኮረ የግንዛቤ መሰጨበጫ ሰልጠና ልደታ በሚገኘው የጠቅላይ ፍርድ ቤት ፍርድ አፈፃፀም ህንፃ ላይ በመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ለሚገኙ የሁሉም ምድብ ችሎት እና የዋናው መስሪያ ቤት የአይሲቲ ቡድን መሪዎች እና የጥገና ባለሙያዎች ከግንቦት 4 እስከ 7 ቀን 2018 ዓ.ም የሚቆይ የአራት ቀናት ስልጠና እየተሰጠ ነው፡፡

“በሕገ መንግሥት ትርጉም የፌዴሬሽን ምክር ቤት ሥልጣን፣ የዳኝነትና የፍትሕ ተቋማት ሚና

29

የኢፌዴሪ ፌዴሬሽን ምክር ቤት እና የፌዴራል ሕግና ፍትሕ ኢንስቲትዩት በሕገ መንግሥት ትርጉም የፌዴሬሽን ምክር ቤት ሥልጣን፣ የዳኝነትና የፍትሕ ተቋማት ሚና በሚል ርዕስ በጋራ ያዘጋጁት የምክክር መድረክ በመካሄድ ላይ ይገኛል።

ለሁለት ቀናት ሲካሄድ የቆየዉ የ9 ወራት የእቅድ አፈፃፀም ግምገማ ተጠናቀቀ።

99

የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት ክቡር አቶ ፉዓድ ኪያር፣ የማኔጅመንት ኮሚቴ አባላት፣ የሁሉም ምድብ ችሎቶች ተጠሪ ዳኞች፣ ዳይሬክተሮች፣ አስተባባሪ ሬጅስትራሮች እና የቡድን መሪዎች በተገኙበት የ2018 በጀት ዓመት የ9 ወራት እቅድ አፈፃፀም ግምገማ ሚያዚያ 26 እና 27 ቀን በቢሾፍቱ ከተማ በቲኬ ሆቴል እና ሪዞርት ተካሄደ::

የመርሀ ግብሩን መክፈቻ ያደረጉት የፍርድ ቤቱ የሰው ሃብት ስራ አመራር ዋና ዳይሬክተሩ የተከበሩ አቶ የምስራች ከተማ በአስተላለፋት የእንኳን ደህና መጣችሁ እና የመርሃግብሩ መክፈቻ መልእክት ባለፋት ዘጠኝ ወራት ውስጥ በተደረገ ርብርብ ስለተገኙ ውጤቶች እና ስለታዩ ክፍተቶች በመግለፅ በኢ.ፌ.ዴ.ሬ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈፃፀሙ ቀርቦ የተገመገመ እና የተሻለ ውጤት የተገኘበት መሆኑን በመግለፅ በውጤቱ ልንበረታታ ይገባል ብለዋል።

ኢ-ፋይሊንግ (e-Filing) ስራ ለመጀመር የሚያስችል ስልጠና ተሰጠ

213

የፌደራል ፍርድ ቤቶች የሚሰጡት የዳኝነት አገልግሎት ቀልጣፋ፣ ዘመናዊ እና ተደራሽ ለማድረግ በርካታ የለውጥ ስራዎች እየሰሩ መሆናቸው ይታወቃል፡፡ ከለውጥ ስራዎች መካከል የዲጂታይዘሽን ስራ ይገኝበታል፡፡ መዝገቦችን እስካን በማድረግ ወደ ዲጅታል የመዝገብ ዓይነት የመቀየር ስራ በአራት ምድብ ችሎቶች በልደታ፣ ንግድና ኢንቨስትመንት፣ አቃቂ ቃሊቲ እና ንፋስ ስልክ ላፍቶ ምድብ ችሎቶች ከመስከረም 2018ዓ/ም ጀምሮ እየተሰራበት የቆየ ሲሆን ወደ ዲጅታል የመዝገብ ዓይነት የተቀየሩ ይግባኝ የሚጠየቅባቸው መዝገቦች ወደ ፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የሚላክበት የኢ-ፋይሊን ሲስተም Electronic Filing (e-Filing System) ወደ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ለመላክ ዝግጅት ሲደረግ ቆይቷል፡፡

አለም አቀፍ ንግድ : የባንክ ዎስትና እና የዲጂታል ባንኪንግ ጋር በተያያዙ ጉዳዬች ላይ ስልጠና መስጠት ተጀመረ ።

31

የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር በመተባበር በ "International Trade, Bank Gurantee እንዲሁም በ Digital Banking" ጋር በተያያዙ ጉዳዮች ላይ ለፍርድ ቤቱ አመራሮች፣ ለ13ቱም ምድብ ችሎት ድሬደዋን ጨምሮ ተጠሪ ዳኞች እንዲሁም ለዳኞች መጋቢት 18 እና 19 ቀን 2018 ዓ.ም ለሁለት ቀን የሚቆይ በኢሊሌ ኢንተርናሽናል ሆቴል ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል።

በስልጠናው መክፈቻ ወ/ሮ ሶስና አለማየሁ የህግ አገልግሎት ዲቪዥን ም/ፕሬዝዳንት ባስተላለፋት መልእክት ንግድ ባንኩ ስራ ላይ ስላዋላቸው የዲጂታል አማራጮች፣ ስለ ህግ ማእቀፎች፣ በዲጂታል የፋይናንስ እንቅስቃሴ ውስጥ ስለሚታዩ የፍትሀብሔር እና የወንጀል ተጠያቂነትን እንዲሁም ባንኮች የሚመሩባቸውን ህግጋቶች ለማሳወቅ ስልጠናው መዘጋጀቱን ገልፀዋል።

ለሁለት ቀናት ሲሰጥ የነበረዉ ስልጠና ተጠናቀቀ

175

የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር በመተባበር በ "International Trade, Bank Gurantee እንዲሁም በ Digital Banking" ጋር በተያያዙ ጉዳዮች ላይ ለፍርድ ቤቱ አመራሮች፣ ለ13ቱም ምድብ ችሎት ድሬደዋን ጨምሮ ተጠሪ ዳኞች እንዲሁም ለዳኞች መጋቢት 18 እና 19 ቀን 2018 ዓ.ም ለሁለት ቀናት ሲሰጥ የነበረዉ ስልጠና ተጠናቀቀ።

ሀገር አቀፍ የዳኝነት እና የፍትህ አካላት የጋራ መድረክ ተጠናቀቀ

181

‎አዲስ አበባ፦ መጋቢት 19/2018 ዓ/ም (የፌዴራል ጠቅላይ ፍ/ቤት)

‎ለሁለት ቀናት ሲካሄድ የቆየው አመታዊ ሀገር አቀፍ የዳኝነት እና የፍትህ አካላት የጋራ የምክክር መድረክ (ጆይንድ አፕ ጀስቲስ ፎረም) የፌዴራልና የክልል የዳኝነትና የፍትህ አካላት የጋራ መድረክ የመግባቢያ ሰነድ የፊርማ ስነ ስርዓት በማከናወን ተጠናቋል።

‎የመግባቢያ ሰነዱ የዳኝነትና የፍትህ አካላት የዕቅድ አፈጻጸም በጋራና በትብብር የሚታይበት ስርዓት መዘርጋት፣ በዘርፉ የሚታዩ ችግሮች ላይ የጋራ አቅጣጫ ማስቀመጥና የተሳለጠ የመረጃ ልውውጥ እንዲኖር ለማስቻል ያለመ መሆኑ ተገልጿል።

ትኩረቱን በባህላዊ የግጭት መፍቻ ዘዴዎች ላይ ያደረገ አህጉራዊ ኮንፍረንስ በመዲናችን አዲስ አበባ በደማቅ ሁኔታ መካሄድ ጀመረ

154

ኢ.ፌ.ዴ.ሪ ፍትሕ ሚኒስቴር ከአጋር አካላት ጋር በመተባበር ያዘጋጀውና ባሕላዊ የግጭት መፍቻ ዘዴዎች በፍትሕ አስተዳደር ሥርዓት ውስጥ ያላቸው ሚናና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ የሚያተኩረው አህጉራዊ ኮንፍረንስ “Strengthening Traditional Dispute Resolution For Access To Justice In Africa” በሚል ርዕስ በመዲናችን አዲስ አበባ የአድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም መጋቢት 16/2018 ዓ.ም መካሄድ ጀምሯል።

የኮንፍረንሱ ተሳታፊዎች በሚኖራቸው የሁለት ቀን ቆይታ በአህጉሪቱ በሚገኙ ባህላዊ የግጭት መፍቻ ዘዴዎች ላይ በጋራ ይወያያሉ፣ ዕርስ በርሳቸው ካላቸው ልምድ ይማማራሉ እንዲሁም ትብብሮችን ይፈጥራል ተብሎ ይታመናል፡፡

የተጠሪ ዳኞች ፎረም !!

179

በፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ሁሉም ምድብ ችሎት ለሚገኙ ተጠሪ ዳኞች መጋቢት 10 ቀን 2018 ዓ∙ም በፍርድ ቤቱ ፕሬዝዳንት ፅህፈት ቤት በሚገኘው የመሰብሰቢያ አዳራሽ የፎረም ዉይይት እና የግንዛቤ ማስጨበጫ መርሃ-ግብር ተከናወነ።

በግንዛቤ ማስጨበጫ መርሃ-ግብሩ የተገኙት የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤቱ ፕሬዝዳንት ክቡር አቶ ፉአድ ኪያር ተጠሪ ዳኞች በየምድብ ችሎቶቻቸው ተቀራራቢ የሆነ አሰራር ለመፍጠር መድረኩ ልምድ የምትለዋወጡበት በመሆኑ በቀጣይነት ጠንክሮ መገናኘት እና መስራት እንደሚገባ በማሳሰብ በተለይ አዲስ ተሿሚ ዳኞችም ሆኑ ሌሎች የፍርድ ቤቱ ባለሙያዎች እና ሰራተኞችን በተሻለ ስነ-ምግባር እና በጥብቅ ዲሲፒሊን ወደ ስራ ማስገባት፣ መከታተል እና መደገፍ እንዲሁም በየምድብ ችሎቱ ባልተከናወኑ ተግባራት ላይ ትኩረት አድርጎ ለተሻለ አፈፃፀም መስራት እንደሚገባ ለዚህም የየምድቡ ተጠሪ ዳኞች ተፅእኖ ፈጣሪ መሆን እንደሚገባቸው እና የተግባቦት /የኮሙኒኬሽን/ ክህሎታቸውን ማዳበር እንደሚያስፈልግ ገልፀዋል።

ፕሬዝዳንቱ የተከበሩ አቶ ፉዓድ ኪያር በየምድብ ችሎቶች ለአስተማሪነት የሚሆኑ መገለጫዎችን በማንሳት በተለይ ከስነ-ምግባር ጋር ተያይዞ በአቤቱታ የሚገለፁ ከመዝገቦች መሰወር፣ ከባለ ጉዳዮች መስተንግዶ ጉድለት፣ ከግልፅ ችሎት ወደኋላ የመመለስ ጅምሮች፣ በሰዓት በአግባቡ አለመጠቀም፣ ሚዛናዊ ሆኖ ነገሮችን ሳይጋነንም እንዲሁም ሳያንስም በልኩ በማየት ተከታትሎ መስራት እንደሚገባ በመርሃ-ግብሩ መክፈቻ መልዕክታቸው አሳስበዋል።`

የፌዴራል ፍርድ ቤቶች አለም አቀፉን የሴቶች ቀን አከበሩ

239

የፌዴራል ፍርድ ቤቶች የዘንድሮ ዓለም አቀፉን የሴቶች ቀን ማርች 8 በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ115ኛ ጊዜ GIVE TO GAIN በሚል መሪ ቃል በሀገር አቀፍ ደረጃ ደግሞ ለ50ኛ ጊዜ "የሴቶች ድምጽ ለዕኩልነት እና ለበለጸገች ኢትዮጵያ "በሚል መሪ ቃል መጋቢት 4 ቀን 2018 ዓ.ም በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት መሰብሰቢያ አዳራሽ ተከብሯል፡፡

123456