የፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አመራሮች ፣ ተጠሪ ዳኞች፣ ዳኞች፣ ዳይሬክተሮች የመቻቻል እና የፍቅር ከተማ በሆነችው በሀረር ከተማ በመገኘት በሀረር ከተማ ውስጥ የሚገኙ ከ1300 ዓመታት በላይ እድሜ ያስቆጠሩ የተለያዩ የታሪክ እና የስልጣኔ ምስክር የሆኑ ቅርሶችን እና የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤትን ጎብኝተዋል፡፡ ሀረር ሀገራችን የብዙ ዘመናት ታሪክ እና ስልጣኔ ባለቤት መሆናን ከሚያመለክቱ ቦታዎች አንዱ ሲሆን ጉብኝቱም ስለ ሀረር በቂ ግንዛቤ ለመያዝ የሚያስችል እድል የፈጠረ ነው፡፡