የኢ-ፍሊት ማኔጅመንት ስልጠና ለአመራሮች ተሰጠ።

78

በተሽከርካሪ ሥምሪት እና አጠቃቀም የሚባክነውን ሃብት ለመቆጣጠር የሚያስችል የኢ-ፍሊት ማኔጅመንት ትግበራ በፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ለማስጀመር ለፍርድ ቤቱ የማኔጅመንት አባላት፣ የየምድብ ችሎት ተጠሪ ዳኞች እና የስራ ክፍል ዳይሬክተሮች ነሐሴ 27 እና 28 ቀን 2018 ዓ.ም ከመንግስት ግዥ እና ንብረት ባለስልጣን በመጡ ባለሙያዎች ስልጠና ተሰጠ።

የፌደራል ፍርድ ቤቶች የአምስት ዓመት (ከ2019 እስከ 2023) ረቂቅ ስትራቴጂያዊ እቅድ ላይ ውይይት ።

102

ፍርድ ቤት አስተባባሪነት ሲዘጋጅ የቆየው 4ኛው የፌደራል ፍርድ ቤቶች የአምስት ዓመት (ከ2019 እስከ 2023) ረቂቅ ስትራቴጂያዊ እቅድ ላይ የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የማኔጅመንት አባላት፣ የምድብ ችሎት ተጠሪ ዳኞች፣ አስተባባሪ ሬጅስትራሮች እና የስራ ክፍሎች ዳይሬክተሮች በተገኙበት ነሐሴ 14 ቀን 2018 ዓ.ም የግብዓት ማሰባሰቢያ ውይይት ተደረገ።

የፌደራል ፍ/ቤቶች የአስተዳደር ሠራተኞች የ2019 በጀት ዓመት የስልጠና እቅድ ላይ ውይይት ተደረገ።

114

የፌደራል ፍርድ ቤቶች የአስተዳደር ሠራተኞች የ2019 በጀት ዓመት የስልጠና እቅድ በተመለከተ የተዘጋጀው የዳሰሳ ጥናት እና እቅድ ለፌ/መ/ደ/ፍ/ቤት የበላይ አመራሮች ቀርቦ ውይይት ተካሄደበት፡፡

የስልጠና እቅዱን ለበላይ አመራሮች ያቀረቡት የፌ/ጠ/ፍ/ቤት የሰው ሀብት ልማት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ አሮን ደጐል ሲሆኑ በጥናት ሠነዱ የ2018 የስልጠና እቅድ አፈፃፀም ግምገማ፣የነበሩ ጠንካራ ጐኖች፣ክፍተቶች እና ያጋጠሙ ችግሮችን በዝርዝር አቅርበዋል፡፡ በተጨማሪም ጥናቱ የተካሄደበትን አግባብ እና የፍላጎት ዳሰሳ መሰረት በማድረግ የተለዩ 21 የስልጠና ርዕሶች እና ሰልጣኞች እቅድ አቅርበዋል፡፡

የዳሰሳ ጥናቱ ከቀረበ በኃላ የፌ/መ/ደ/ፍ/ቤት የበላይ አመራሮች በርከታ አስተያየት እና ጥያቄዎችን ያቀረቡ ሲሆን በቀረበው ሰነድ ላይ ሰፊ ውይይት ተካሂዶል፡፡

አዲሱ የወንጀል ስነ-ስርዓት እና የማስረጃ ህግ በፌ/መ/ደ/ፍ/ቤት ሊያስከትል የሚችለዉን አተገባበርና ለውጥ በተመለከተ የጥናት ሠነድ ቀረበ !

88

አዲሱ የወንጀል ስነ-ስርዓት እና የማስረጃ ህግ አዋጅ ቁጥር 1410/18 መፅደቁን ተከትሎ በርካታ አዳዲስ አሠራሮች በአዋጁ የተካተቱ ከመሆኑም በላይ በርካታ የወንጀል ድንጋጌዎች ወደ ፌ/መ/ደ/ፍ/ቤት መውረዳቸዉ እና የአደረጃጀት እና አሠራር ለውጥ መካተቱ ይታወቃል፡፡

በመድን ሽፋን (Insurance Coverage ) ህግ እና አሰራር ላይ ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል።

121

የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ከኢትዮጵያ መድን ሰጪዎች ማህበር ጋር በመተባበር ለሁለት ቀናት (ነሐሴ 2 እና 3 ) የሚቆይ በመድን ሽፋን (Insurance Coverage ) ህግ እና አሰራር ላይ የታኮረ ስልጠና በቢሾፍቱ ከተማ እየሰጠ ይገኛል ።

በስልጠናዉ የፍርድ ቤቱ ከፍተኛ አመራሮች፣ የንግድ እና ኢንቨስትመንት ምድብ ችሎት ሁሉም ዳኞች እና የምድብ ችሎቶች ተጠሪ ዳኞቸ የተገኙ ሲሆን ስልጠናዉ በዋናነት ከኢንሹራንስ ጋር የተያያዙ ህጎች እና አከራካሪ ጉዳዮች ላይ እየተሰጠ ነዉ ።

በድህረ-ውሳኔ መዛግብት ምርመራ እና በ2018 በጀት ዓመት አፈፃፀም ሪፖርት ላይ ከፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ሁሉም ዳኞች ጋር ውይይት ተደረገ።

81

በድህረ-ውሳኔ መዛግብት ምርመራ እና በ2018 በጀት ዓመት አፈፃፀም ሪፖርት ላይ ሁሉም የፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ዳኞች በተገኙበት ሐምሌ 25 ቀን 2018 ዓ.ም በካፒታል አዲስ አበባ ሆቴል ውይይት ተደረገ።

አዲስ ለተሾሙ ረዳት ዳኞች የትውውቅ እና የስልጠና መርሃ-ግብር ተዘጋጀ።

101

የፌደራል ዳኞች አስተዳደር ጉባኤ ሰኔ 12 ቀን 2018 ዓ.ም ባደረገው ስብሰባ ለፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በርካታ ረዳት ዳኞችን ከሐምሌ 1 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ መሾሙ ይታወቃል።

ይህንንም ተከትሎ የፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የተሾሙለትን ሁሉንም ረዳት ዳኞች በ13 ምድብ ችሎቶች በመደልደል ስራ ያስጀመረ ሲሆን በዛሬዉ እለት ደግሞ የትውውቅ፣ የስራ አቅጣጫ እና አጫጭር ስልጠናዎችን ሰጥቷል።

በሴቶች፣ህፃናት እና አካል ጉዳተኞች ዙሪያ የሚሰሩ የራስ አገዝ (CoSAP) ድርጅቶች ህብረት የመሠረቱት ተግባር ተኮር ማህበረሰብ (Community of practice) የተሰኘ ቅንጅት በፌ/መ/ደ/ፍ/ቤት በመገኘት የውይይት እና ጉብኝት መርሀ-ግብር አካሄዷል፡፡

61

ይህ ቅንጅት በሴቶች፣ህፃናት፣እና አካል ጉዳተኞች ዙሪያ የሚሠሩ አስራ አራት ማህበራት ያቀፈ ሲሆን ለጉዳት ተጋላጭ በሆኑ ማህበረሰቦች ጋር በተያያዘ በፌ/መ/ደ/ፍ/ቤት እየተሰሩ ስላሉ ስራዎች ግንዛቤ በመውሰድ እና በቀጣይ በትብብር ለመስራት በሚያስችሉ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል፡፡

በውይይቱ ላይ የፌ/መ/ደ/ፍ/ቤት ኘሬዝዳንት ክቡር አቶ ፉአድ ኪያር የተገኙ ሲሆን ፍ/ቤቱ ከሴቶች እና ህፃናት ጋር በተያያዘ እየሠሯቸዉ ያሉትን በርካታ ስራዎች በመግለፅ ለጉዳት ተጋላጭ ለሆኑ ማህበረሰብ ክፍሎችን ከፍትህ ስርዓቱ ጋር በማገናኘት መደገፍ እና መጠበቅ እንደሚያስፈልግ በመግለፅ ለዚህ ደግሞ የተለያዩ ተቋማት ትብብር ወሳኝ መሆኑን ገልፀዋል፡፡

የአመራሮች የምክክር መድረክ ተካሄደ ፡፡

22

የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት የበላይ አመራሮች፣የምድብ ችሎት ተጠሪ ዳኞች እና አስተባባሪ ሬጅስትራሮች በ2018 በጀት ዓመት አፈፃፀም እና በቀጣይ የክረምት ወራት በሚሠሩ ትኩረት የሚሹ ጉዳዬች ዙሪያ በዛሬው እለት ምክክር ተደርጓል፡፡

የማህበረሰብ ተኮር ፍትህ ( Community Based Justice )ወይይት ተደረገ፡፡

111

የፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የሚያከናውነውን የፍርድ ቤት መር አስማሚነት (Court-annexed Mediation) የአሠራር ሥርዓት በድሬደዋ ከተማ አስተዳደር ክልል ውስጥ ከሚገኙትና ማኅበረሰባዊ መስተጋብሩን በበጎ ከሚያጸኑት የባህልና የሃይማኖት የሽምግልና እሴቶች ጋር አቀናጅቶ ለመምራት በሁለቱ ተቋማት መካከል ግንቦት 27 ቀን 2018 ዓ.ም ፍሬያማ የጋራ የውይይት መድረክ መካሄዱ ይታወሳል፡፡

ለረዳት ዳኞች ለሁለት ቀናት የሚቆይ ስልጠና ተሰጠ:;

116

የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ከፌደራል ህግ እና ፍትህ ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር ለረዳት ዳኞች የአስማሚነት ክህሎት ማዳበሪያ ስልጠና ከሰኔ 19 እስከ 20 ቀን 2018 ዓ.ም ለሁለት ቀናት የሚቆይ በአዲስ አበባ ድሪምላይነር ሆቴል እየተሰጠ ይገኛል።

የዳኞች ፎረም

240

የንግድ እና ኢንቬስትመንት ምድብ ችሎት የዳኞች ፎረም ተካሄደ፡፡

የፌዴራል መጀመረያ ደረጃ ፍረድ ቤት የንግድ እና ኢንቬስትመንት ምድብ ችሎት የግልግል ዳኝነት ህጉ እና አተጋባበሩን አሰመልክቶ በፍርድ ቤቶች የሚያጋጥሙ ጉዳዮች ላይ የሚታዩ ክፍተቶች እና መፍትሄዎችን በተመለከተ ሰኔ 16, ቀን 2018 ዓ.ም በንግድ እና ኢንቬሰትመንት ምድብ ቸሎት አሰማሚ ቢሮ ውሰጥ ሁሉም ዳኞች በተገኙበት ውይይት ተካሄደ፡፡

የንግድ እና ኢንቬስትመንት ምድብ ችሎት የዳኞች ፎረም ተካሄደ፡፡

የፌዴራል መጀመረያ ደረጃ ፍረድ ቤት የንግድ እና ኢንቬስትመንት ምድብ ችሎት የግልግል ዳኝነት ህጉ እና አተጋባበሩን አሰመልክቶ በፍርድ ቤቶች የሚያጋጥሙ ጉዳዮች ላይ የሚታዩ ክፍተቶች እና መፍትሄዎችን በተመለከተ ሰኔ 16, ቀን 2018 ዓ.ም በንግድ እና ኢንቬሰትመንት ምድብ ቸሎት አሰማሚ ቢሮ ውሰጥ ሁሉም ዳኞች በተገኙበት ውይይት ተካሄደ፡፡

የ2018 ዓ.ም የባለድርሻ አካላት መድረክ ተካሄደ።

237

የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ላለፋት ተከታታይ ዓመታት እንደሚያከናውነው ሁሉ የዘንድሮ የ2018 በጀት ዓመት የባለድርሻ አካላት የውይይት መድረኩን ሰኔ 6 ቀን 2018 ዓ.ም አዲስ አበባ በሚገኘው ኢንተር ሌግዠሪ ሆቴል አካሄደ። በዘንድሮው የባለድርሻ አካላት መድረክ ፍርድ ቤቱ ለመጀመሪያ ጊዜ ያስጠናውን የ2017 ዓ.ም "የድህረ ውሳኔ መዛግብት ምርመራ" ሪፖርት ሰነድ ያቀረበ ሲሆን በቀረበው ሪፖርቱ ላይ ሰፊ ውይይት ተደርጎ ግብዓት ማግኘት ተችሏል።

የፍርድ ቤት መር አስማሚነትን ከባህል እና ሽምግልና ስርአት እንዲሁም ከሃይማኖት አባቶች ጋር ለማቀናጀት የምክክር መድረክ በድሬደዋ ከተማ ተካሄደ።

232

የፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት እያከናወነ ያለውን የፍርድ ቤት መር አስማሚነት የበለጠ ለማጠናከርና የህብረተሰቡን ተሳትፎ ለማሳደግ ይጠቅም ዘንድ ከድሬደዋ ከተማ ከንቲባ ጽ/ቤት ጋር በመተባበር በከተማ አስተዳደሩ ካሉ የባህል ሽማግሌዎች (አባ ገዳና ኡጋዝ) እንዲሁም ከሃይማኖት አባቶች ጋር የውይይት መድረክ ተዘጋጀ ። በመድረኩም የሀገር ሽማግሌዎችና የሀይማኖት አባቶች ወደ ፍርድ ቤቱ የፍርድ ቤት መር አስማሚነት ትግበራ ሥርዓት በመግባት አገልግሎት የሚሰጡበትና የፍትህ ተደራሽነትን በሚያረጋግጡበት መንገድ ላይ ውይይት ተደርጓል።

ተጫራቾች ተጋብዛችኋል !!

301

የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ለዋና መስሪያ ቤት እና በኢፌ.ዴ.ሪ ፍትህ ሚኒስቴር ጠቅላይ ዐቃቢ ህግ ዘርፍ ለልደታ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት በአዲስ የሚገነቡ ህንፃዎች (2B+G+11 እና 2B+G+6) በተመለከተ የዲዛይን የአፈር ምርምራ እናየማማከር ስራውን በማጠናቀቅ የግንባታ ሂደቱን በግልጽ ጨረታ አውጥቷል፡፡

1234567